በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
አሐዱ አምላክ አሜን
ሦስቱ ዛፎች
የአራዊት መጠለያ ከሆነው ጥቅጥቅ ካለው ደን መካከል ከፍ ብለው የሚታዩ ሦስት ዛፎች ነበሩ፡፡ እነዚህ ዛፎች ካሉበት ሆነው እንዳች ጠቃሚ ውይይት እያደረጉ ነው፡፡ እነዚህ ዛፎች ወደ ፊት ምን መሆን እንደሚፈልጉ የልባቸውን ምኞት በግልጽ እየተነጋገሩ ነበር፡፡
“አኔ መቼስ” አለ አንደኛው ዛፍ “ፈጣሪዬ ቢፈቅድና ከአናጺዎች ምሳር ቢሠውረኝ ምኞቴ ትልቅ ደረጃ ላይ መድረስ ነው፡፡” አለ፡፡ ሁለተኛው ዛፍ በመገረም “ዛፍ ካልተቆረጠና ለአንድ ሥራ ካልዋለ ዝም ብሎ ቢቆም አርጅቶ ከመውደቅ ሌላ ምን ትልቅ ደረጃ ላይ ሊደርስ ይችላል” ብሎ ጠየቀው፡፡ “አይ አንተ እንዳልከው አርጅቶ መውደቅ ሳይሆን የእኔ ምኞት የዕፅዋት ሁሉ ንጉሥ መሆንና ከፍ ከፍ ብሎ መታየት ነው፡፡