Saturday, September 14, 2013

ሦስቱ ዛፎች



በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
ሦስቱ ዛፎች


የአራዊት መጠለያ ከሆነው ጥቅጥቅ ካለው ደን መካከል ከፍ ብለው የሚታዩ ሦስት ዛፎች ነበሩ፡፡ እነዚህ ዛፎች ካሉበት ሆነው እንዳች ጠቃሚ ውይይት እያደረጉ ነው፡፡ እነዚህ ዛፎች ወደ ፊት ምን መሆን እንደሚፈልጉ የልባቸውን ምኞት በግልጽ እየተነጋገሩ ነበር፡፡

“አኔ መቼስ” አለ አንደኛው ዛፍ “ፈጣሪዬ ቢፈቅድና ከአናጺዎች ምሳር ቢሠውረኝ ምኞቴ ትልቅ ደረጃ ላይ መድረስ ነው፡፡” አለ፡፡ ሁለተኛው ዛፍ በመገረም “ዛፍ ካልተቆረጠና ለአንድ ሥራ ካልዋለ ዝም ብሎ ቢቆም አርጅቶ ከመውደቅ ሌላ ምን ትልቅ ደረጃ ላይ ሊደርስ ይችላል” ብሎ ጠየቀው፡፡ “አይ አንተ እንዳልከው አርጅቶ መውደቅ ሳይሆን የእኔ ምኞት የዕፅዋት ሁሉ ንጉሥ መሆንና ከፍ ከፍ ብሎ መታየት ነው፡፡ 

Friday, August 17, 2012

ደብረ ታቦር


ሠናይ ለነ ህልዎዝየ
በዚህ መሆን ለኛ መልካም ነው፡፡                       
       በጎፋ ቤዛ/ብዙኃን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ካቴድራል መዝገበ ምሕረት በህፃናት ክፍሉ የተዘጋጀ፡፡
      ይህንን ቃል የተናገረው ቅዱስ ጴጥሮስ ነው፡፡ ጴጥሮስ ማለት መሠረቱ የማይነቃነቅ አለት ማለት ነው፡፡ ማር 3፡6 የሐዋርት ሁሉ ተጠሪ እንዲሁም የሚስጢር ሐዋርያ ከሚባሉት አንዱ ነው ጴጥሮስ ዓሳ አስጋሪነት (አሳ አጥማጅነት)ከወንድሙ እንድሪያስ ጋር በስተርጅና የተጠራ ሐዋር ነው፡፡ ከጌታችን እግር ስር በመሆን ታዕምሩና ትምህረቱ ሁሉ ይከታተል የነበረ ሐዋሪያን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የኢያእሮስን ልጅ ሲያስነሳ አላዛርን ከሙታን ሲስነሳ በስሞን ቤት መዐድ ተቀምጦ የኦሪትን መስዋዕት ሽሮ የአዲስ ኪዳንን ሰተካ ጴጥሮስ ከጌታችን ጋር ነበረ፡፡ ከላ የተናገረውን ቃል ከሐዋርት መካከል ሦስቱ የምስጢር ሐዋር የሚባሉ ጴጥሮስ ያቆብ እና ዮሐንስ ይዞ ወደ ረዥም ተራራ አወጣቸው ከቤሔረ ሄዋን ነብዩ ኤሊያስን ከብሔረ ሙታን ደግሞ ነቢዩ ሙሴ እንዲሁም ካገባ ነቢዩ ሙሴን ከደናግል ነቢዩ ኤሊያስን አመጣ በፊታቸውም ተለወጠ ፊቱም እንደ ፀሐይ ልብሱም እንደብርሃን ነጭ ሆነ፡፡ ኤልያስና ሜሴን ከፈጣሪቸው ጋር ሲነጋገሩ ታየዋቸው ከነቢያት ሁለት ከሐዋርያት ደግሞ ሦስት በድምሩ አምስት አንድ ላይ ሆነው ታዩ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ህንን ሲያይ እንዲህ አለ ‹‹ ሰና ለነ ህልዋዝየ›› በዚህ መኖር ለኛ መልካም ነው፡፡ እሱም ገና ህንን ሲናገር ብሩህ ደመና መጥቶ ጋረዳቸው በእነርሱም ደስ የሚለኝ ልጄ ይሄ ነው፡፡ እሱን ስሙት የሚል ቃል መጣ ደቀማዛሙርቱ ይህንን ሰምተው በግንባራቸው ወደቁ እጅግ ፈርተው ነበር፡፤ ጌታችንም ቀርቦ ዳሰሳቸው ተነሱ አትፍረም አላቸው፡፡አይናቸውንም አቅንተው አዩ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ በቀር ማንም አላገኙም በዚህም ነገር ጴጥሮስ ዮሐንስ ያዕቆብ ተደሰቱ፡፡ ከዚህ በኋላ የሚስደስት ነገር የለምና ሁል ጊዜ የሰው ልጅ ከእግዚአብሔር ጋር ሲኖር ይደሰታል፡፡ ከመከራና ከዳቢሎስ ፈተና ድል ያደርጋል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢሱስ ክርስቶስ ወደ ተራራ ሦስቱን ሠዋርያ እንዲሁም ሙሴንና ኤሊያስን ማምጣቱ ምስጢር አለው፡፡
ተራራ የቤተክርስቲያን ምሣሌ ነው፡፡

Tuesday, June 19, 2012

የመላዕክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል

ሚካኤል ማለት ‹እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው; ማለት ነው፡፡ ይህም የእግዚአብሔርን ገናንነትና እሱን የሚመስል አምላክ እንደሌለ የሚያመለክት ነው እንደ እግዚአብሔር ያለ ቅዱስ ንጹሕ ርህሩህ ኃይል ረቂቅ ማነው መልሱ የለም ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል የስሙ ዘርፍ ሆነው የሚጨመሩ መጠሪያዎች አሉት እነዚህም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠውን የባለሟልነት ክብር የሚገልጹ ናቸው፡፡ ይኸውም መልአከ ኃይል፣ መጋቤ ብሉይ፣ መልአከ ምክሩ…ናቸው፡፡ መልአከ ኃይል የተባለው እግዚአብሔር በሱ አማካይነት ታላላቅ ሥራዎችን በመሥራት ኃይሉን ስለገለጸ$ ዲያብሎስን ከነሠራዊቱ ስላሸነፈ ነው፡፡ መጋቤ ብሉይ የተባለበት ምክንያት በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከእግዚአብሔር እየተላከ ብዙ ታላላቅ ሥራዎችን የሠራ በመሆኑ ነው፡፡


መልአከ ምክር ወይም የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ የተባለበት ምክንያት እግዚአብሔርን በምክሩ ይረዳዋል ለማለት ሳይሆን እግዚአብሔር የሚሠራውን ሥራ ለወዳጁ ለቅዱስ ሚካኤል ይገልጽለታል በሱም አማካኝነት ይሠራል ለማለት ነው፡፡

ቅዱስ ሚካኤል በመጽሐፍ ቅዱስ

Saturday, June 16, 2012

ነገረ ማርያም

«አልብኪ ነውር ወኢምንትኒ ላዕሌኪ፤» መኃ 4:7
                    
                                                                                ከኪዳነምህረት ድህረ ገፅ ላይ የተወሰደ
                                                                                         http://kidanemhret.org              
 
የትንቢተ ነቢያት ማረፊያ ፡-የስብከተ ሐዋርያት መነሻ.የሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምሥጢር ነገረ ማርያም ነው፡፡ ያለ ነገረ ማርያም ነገረ ክርስቶስን መናገር አይቻልም፡፡ በክርስትና ሃይማኖት ታሪክ የተነሡ አያሌ መናፍቃን የመጀመሪያ ችግራቸው የነገረ ማርያምን አማናዊ ትምህርት መቀበል ነበር ፡፡ ያም ችግራቸው ክርስቶስን በትክክል እንዳያምኑት አድርጓቸዋል፡፡ በነገረ ማርያም ላይ የተጣራ ትምህርትና እምነት ቢኖራቸው ኖሮ ለኑፋቄ አይጋለጡም ነበር ፡፡ ንስጥሮስ፡- «አምላክ ወልደ አምላክ» ብሎ በክርስቶስ ለማመን የተሳነው « ወላዲተ አምላክ . ወላዲተ ቃል. እመ እግዚአብሔር » ብሎ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ለማመን በመቸገሩ ነበር፡፡

ነገረ ማርያምን ከነገረ ክርስቶስ መለየት አይቻልም ፡፡ የተዋሐደ ነው ፡፡ ስለ እመቤታችንየሚነገረው ክፉም ሆነ በጎ ክርስቶስን ይነካዋል፡፡ የእግዚአብሔርን የማዳን ሥራበምንናገርበት ጊዜ እመቤታችንን ወደ ጎን መተው አይቻልምና፡፡ ምክንያቱም ወልዳያስገኘች. አዝላ የተሰደደች. በማስተማር ጊዜው ከአገር አገር አብራው የተንከራተተችናትና ፡፡ በተሰቀለበት ዕለትም ከእግረ መስቀሉ አልተለየችም፡፡ በአጠቃላይ አነጋገርምክንያተ ድኂን አድርጓታል፡፡

Saturday, June 9, 2012

118ኛው የግብጽ ፓትርያርክ

 
ዳንኤል ክብረት እይታዎች የተወሰደ
117ኛው የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ታላቁ አባት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ 3 ሲያርፉ ዓለም በሙሉ ነበር ኀዘኑን የገለጠው፡፡ ክርስቲያኑና ሙስሊሙ፣ ቡድሂስቱና ሺንቶይስቱ፣ የሚያምነውና የማያምነው፣ የቻይናና የአሜሪካ ፖለቲከኞች፣ አንድ ሆነው በአቡነ ሺኖዳ ዕረፍት አዝነው ነበር፡፡
Coptic patriarchs
የእርሳቸውን ዕረፍት ተከትሎም የግብጽ ቤተ ክርሰቲያን እንዲህ ዓለምን በፍቅር አንድ አድርገው የሚገዙ ሌላ አባት ታገኝ ይሆን? የሚለው ጥያቄ ግብጻውያን ምእመናንን ብቻ ሳይሆን ሌሎችንም ያሳሰበ ነበር፡፡ የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ለዚህ ጥያቄ መልስ ለመስጠት ዝግጅቷን ጀምአመራረጥ ራለች፡፡ በቤተ ክርስቲያኒቱ የአዲስ ፓትርያርክ ሥርዓት እጅግ የሚያስደስት፣ ለክርክርና ለሐሜት በር የሚዘጋ፣ አባቶችንና ምእመ ናንን የሚያሳትፍ፤ መንፈሳዊነቱንም የተሞላ ነው፡፡

Tuesday, May 22, 2012

“መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን፡- መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው” /መዝ.86፥1/
በዲ/ን ዮሴፍ ይኩኖአምላክ
http://kidanemhret.org
የተወሰደ


ይህ ቃል የእመቤታችንን አያቶቿን የቀደሙ ወላጆቿን ንጽሕና፣ ቅድስና፣ ክብር አስመልክቶ ቅዱስ ዳዊት የተናገረው የምስክርነት ቃል ነው፡፡ ይህ ምስክርነት አካላዊ ቃል እግዚአብሔር ወልድ ለኩነተ ሥጋ የመረጣት ቅድስት ድንግል ማርያም ወላጆቿ ንጹሐን፣ ቅዱሳን መሆናቸውን ያስረዳል፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም ሲመላለስ፡- “መልካም ዛፍ ሁሉ መልካም ፍሬን ያፈራል፤ ክፉ ዛፍም ክፉ ፍሬን ያፈራል፡፡ መልካምም ዛፍ ክፉ ፍሬን ማፍራት፥ ክፉ ዛፍም መልካም ፍሬን ማፍራት አይችልም” ማቴ.7፥17-18፡፡ በማለት እንደተናገረው እመቤታችን ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም የተገኘችባቸው ወላጆቿ ሁሉ ቅዱሳን ንጹሐን፣ እግዚአብሔርን የሚወዱና የሚያከብሩ መሆናቸውን ልብ ይሏል፡፡ ለመሆኑ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የዘር ሐረግና የትውልድ ታሪኳ ምን ይመስላል?